Pages

Thursday, July 24, 2014

የአሜሪካ የበረራ መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ በኩል በሚያቋርጡ በረራዎች ላይ ማስጠንቀቂያ አወጣ


ሐምሌ ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መስሪያ ቤቱ በመግለጫው በሰሜን ኢትዮጵያ  ከ12 ዲግሪ የትይዩ መስመሮች እስከ ኤትዮ ኤርትራ ድንበር ባለው የአየር ክልል ምንም
አይነት በረራ እንዳይካሄድ መክሯል። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት በዚሁ ክልል የሚያልፉ የንግድም ሆነ ሌሎች አውሮፓላኖችን ሊመታ እንደሚችል አስጠንቅቋል።
የአሜሪካ መንግስት ማስጠንቀቂያ ካወጣባቸው የአፍሪካ አገራት መካከል ኬንያ እና ሶማሊያ ይጠቀሳሉ።
የአሜሪካ አቪየሽን እገዳ የጣለበት የሰሜኑ ክፍል የትግራይ ክልልን የሚሸፍን ነው። በዚህ አካባቢ ምንም አይነት በረራ እንዳይካሄድ መባሉ ብዙ አስተያየቶችን እንዲሰጡ እያደረገ ነው።

No comments:

Post a Comment