Pages

Thursday, October 30, 2014

የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ላለፉት 3 ወራት ያሰለጠናቸውን የአምስተኛ ዙር ታጋዮች አስመረቀ ።

የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ለ 90 ቀናት በተከታታይ በወታደራዊ፣ ፖለቲካዊ እና የመረጃ እና ደህንነት ትምህርቶች ያሰለጠናቸውን ታጋዮች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተለያዩ የተቃዋሚ ድርጅቶች ተወካዮች በተገኙበት በደመቀ  ሁኔታ  አስመርቀ። 
ህዝባዊ ሃይሉ ከዚህ በፊት 4 ተከታታይ ዙሮችን ያስመረቀ ሲሆን የዛሬው ለአምስተኛ ጊዜ ነው። በምረቃ  ስነስርዓቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የህዝባዊ ሃይሉ ዋና አዛዥ ኮማንደር አሰፋ ማሩ ‘’ህዝባዊ  ሃይላችን በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ዘረኛና አፋኝ የወያኔ ስርዓት ከህዝብ እና ከሃገራችን ጫንቃ ላይ አስወግዶ በምትኩ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት ከተመሰረተ ጀምሮ ባለፉት ጊዚያት በርካታ ስራወችን  በመስራት አስተማማኝ ድርጅታዊ አቋም ላይ ይገኛል’’ ብለዋል። 
ኮማንደሩ አያያዘውም ‘’ይህን የአምስተኛ ዙር ምርቃት ከቀደምቶቹ የሚለየው የኢትዮጲያ ህዝብ አርበኞች ግንባር፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ እና  የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ተዋህደው ባንድ ድርጅት ጥላ ስር ትግላቸውን አስተባብረው ለመታገል የሚያደርጉትን የውህደት ሂደት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ያደረሱበት ወቅት ላይ መደረጉነው’ ብለዋል። በተጨማሪም ‘’ይህ የህዝባዊ ሃይላችን ስልጠና በግንቦት ሰባት ስም ከሚደረጉት ስልጠናወች የመጨረሻው ይሆናል ብለዋል።

No comments:

Post a Comment