Pages

Pages

Saturday, April 19, 2014

ህገ ወጥ አሰራሮችን ያጋለጡ መምህራን ታሰሩ

 

ሚያዚያ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ስሙ ቤላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው የህብረት ፍሬ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት መምህራን የሆኑት መ/ር ጥላሁን በዙ እና መ/ር አዳም ዘውዱ በት/ቤቱ እየተከናወነ ያለዉን ህገ-ወጥ አሰራር በመቃወማቸው እንዲሁም ለፌደራሉ ፀረ-ሙሰና ኮሚሽን ጥቆማ በማድረጋቸው፣ ወንጀል ሰርተዋል በሚል ከተጠረጠሩት ጋር አብረው እንዲታሰሩ መደረጉን ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ መምህራን ገልጸዋል።
የየካ ክ/ከተማ የመምህራን ልማት የስራ ሂደት ባለቤት አቶ ሽመልስ መምህራኑ መታሰራቸውን አረጋግጠው፣ ለምን እንደታሰሩ  እንደማውያቁና ጉዳዩ በፖሊስ የተያዘ በመሆኑ የፖሊስን ምርመራ መጠበቅ እንደሚሻል ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment